Jeremiah 50:33 — Compare Translations
13 translations compared side by side
Amharic (Tigrigna: Contemporary Tigrinya Bible 2024)
እግዚኣብሄር ጐይታ ሰራዊት ከምዚ ይብል፡ ደቂ እስራኤልን ደቂ ይሁዳን ብሓባር ተገፊዖም፡ ኵሎም እቶም ከም ምሩኻት ዝመርሕዎም ድማ ሒዞሞም። ንሳቶም ድማ ምፍናው ኣብዮም።
Amharic 2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ “የእስራኤል ልጆችና የይሁዳ ልጆች በአንድነት ተገፍተዋል፤ የማረኩአቸውም ሁሉ በኀይል ይይዙአቸዋል፤ ይለቅቁአቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።
Amharic Bible (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የእስራኤል ልጆችና የይሁዳ ልጆች በአንድነት ተገፍተዋል፥ የማረኳቸውም ሁሉ በኃይል ይይዙአቸዋል፥ ይለቅቁአቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።
Amharic Catholic Version (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
የሠራዊት ጌታ እንዲህ ይላል፦ የእስራኤል ልጆችና የይሁዳ ልጆች በአንድነት ተጨቊነዋል፥ የማረኳቸውም ሁሉ በኃይል ይዘዋቸዋል፥ እነርሱንም ለመልቀቅ እንቢ ብለዋል።
Amharic Dawro DFBE (ጌሻ ማጻፋ) No Year
ኡባፐ ዎልቃማ መና ጎዳይ ሀዋዳን ያጌ፤ “እስራኤልያ አሳይነ ይሁዳ አሳይ እትፐ ናቀቴዳ። ኡንቱንታ ኦሞዲደ አፌዳዋንቱ ኡንቱንታ ዎልቃፐ ምንስ ኦይቄድኖ፤ የደናን ድጌድኖ።
Amharic Dawro DFBLVL (Geeshsha Mas'aafaa)
Ubbaappe Wolk'k'aama Med'inaa Goday hawaadan yaagee; «Israa'eeliyaa asaynne Yihudaa Asay ittippe naak'etteedda. Unttuntta omooddiide afeeddawanttu unttuntta wolk'k'appe minissi oyk'k'eeddino; yeddennan diggeeddino.
Amharic Gamo (Geeshsha Maxaafa)
GODAY Ubbaafe Wolqqama Xoossay, «Isra7eele asaynne Yuhuda asay issi bolla qohettides; di7idayti ubbay istta minththi oykkida; istta yeddanaas ixxida.
Amharic Gamo (ጋሞ ማጻፋ)
ጎዳይ ኡባፌ ዎልቃማ ጾሳይ፥ «ኢስራኤሌ ኣሳይኔ ዩሁዳ ኣሳይ ኢሲ ቦላ ቆሄቲዴስ፤ ዲኢዳይቲ ኡባይ ኢስታ ሚን ኦይኪዳ፤ ኢስታ ዬዳናስ ኢጺዳ።
Amharic Gofa GFBEVF (ጌሻ ማፃፋ)
ኡባፈ ዎልቃማ ጎዳይ ሀይሳዳ ያጌስ፦ “እስራኤለ አሳይነ ይሁዳ አሳይ ኡንኤትዶሶና። ኤንታ ድእድ ኤፍዳይሳት ኤንታ ምንድ ኦይክዶሶና፤ ኤንታ የደናዉ ኮይቦኮና።
Amharic Gofa GFBLVF (Geeshsha Maxaafa)
Ubbaafe Wolqaama Goday haysada yaagees: “Isra7eele asaynne Yihuda asay un7etidosona. Enta di77idi efidaysati enta minthidi oykidosona; enta yeddenaw koybookona.
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣ በአንድነት ተጨቍነዋል፤ የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤ ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “የእስራኤልና የይሁዳ ሕዝብ ተጨቊነዋል፤ ማርከው የወሰዱአቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤ ሊለቁአቸውም አልፈለጉም።
Amharic Tigrinya (መፅሓፍ ቅዱስ)
ጐይታ ሰራዊት እግዚኣብሄር ከምዙይ ይብል ኣሎ፦ “ህዝቢ እስራኤልን ህዝቢ ይሁዳን፥ ብሓባር ተገፊዖም እዮም፤ እቶም ዝማረኽዎም ከዓ ብፅኑዕ ሓዝዎም፤ ከይሰድዎም ድማ ኣበዩ።