bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
/
Job 28
Job 28
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
← Chapter 27
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 29 →
1
“የብር ማዕድን የሚወጣበት፣ ወርቅም የሚነጠርበት ስፍራ አለ።
2
ብረት ከመሬት ውስጥ ይገኛል፤ መዳብም ከማዕድን ድንጋይ ቀልጦ ይወጣል።
3
ሰው፣ እስከ ጨለማ መጨረሻ ይዘልቃል፤ ከድቅድቅ ጨለማ የማዕድን ድንጋይ ለማግኘት፣ እስከ ውስጠኛው ዋሻ ገብቶ ይፈልጋል።
4
የሰው እግር ረግጦት በማያውቅበት ስፍራ፣ ከሰዎች መኖሪያ ርቆ መውረጃ ጕድጓድ ይቈፍራል፤ ሰው በሌለበት ቦታ ይንጠላጠላል፤ ይወዛወዛል።
5
ከላይዋ ምግብን የምታስገኝ ምድር፣ ከታች በእሳት እንደሚሆን ትለዋወጣለች።
6
ሰንፔር ከዐለቷ ይወጣል፤ ከዐፈሯም የወርቅ አንኳር ይገኛል።
7
ያን መንገድ ጭልፊት አያውቀውም፤ የአሞራም ዐይን አላየውም፣
8
ኵሩ አራዊት አልረገጡትም፤ አንበሳም በዚያ አላለፈም።
9
ሰው እጁን በቡላድ ድንጋይ ላይ ያነሣል፤ ተራሮችንም ከሥር ይገለብጣል።
10
በድንጋይ ውስጥ መተላለፊያ ያበጃል፤ ዐይኖቹም የከበሩ ነገሮችን ሁሉ ያያሉ።
11
የወንዞችን ምንጭ ይበረብራል፤ የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።
12
“ነገር ግን ጥበብ ከወዴት ትገኛለች? ማስተዋልስ መኖሪያዋ የት ነው?
13
ሰው ዋጋዋን አያውቅም፤ በሕያዋንም ምድር አትገኝም።
14
ውቅያኖስ፣ ‘በእኔ ውስጥ የለችም’ ይላል፤ ባሕርም፣ ‘በእኔ ዘንድ አይደለችም’ ይላል።
15
ንጹሕ ወርቅ ሊገዛት አይችልም፤ ዋጋዋም በብር አይመዘንም።
16
በኦፊር ወርቅ፣ በከበረም መረግድና በሰንፔር አትገመትም።
17
ወርቅም ብርሌም አይወዳደሯትም፤ በወርቅ ጌጥም አትለወጥም።
18
ዛጐልና አልማዝ ከቍጥር አይገቡም፤ የጥበብ ዋጋ ከቀይ ዕንቍም ይበልጣል።
19
የኢትዮጵያ ቶጳዝዮን ሊስተካከላት አይችልም፤ ዋጋዋም በንጹሕ ወርቅ አይተመንም።
20
“ታዲያ፣ ጥበብ ከወዴት ትመጣለች? ማስተዋልስ የት ትገኛለች?
21
ከሕያዋን ፍጥረታት ዐይን ሁሉ ተሰውራለች፤ ከሰማይ ወፎችም ተሸሽጋለች።
22
ጥፋትና ሞት፣ ‘ወሬዋን ብቻ ሰማን’ ይላሉ።
23
ወደ እርሷ የሚወስደውን መንገድ የሚረዳ፣ መኖሪያዋንም የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤
24
እርሱ የምድርን ዳርቻ ይመለከታልና፤ ከሰማይ በታች ያለውንም ሁሉ ያያል።
25
ለነፋስ ኀይልን በሰጠ ጊዜ፣ የውሆችን መጠን በለካ ጊዜ፣
26
ለዝናብ ሥርዐትን፣ ለነጐድጓድም መንገድን ባበጀ ጊዜ፣
27
በዚያን ጊዜ ጥበብን ተመለከታት፤ ገመገማትም፤ አጸናት፤ መረመራትም።
28
ከዚያም ሰውን፣ ‘እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብ ነው፤ ከክፋትም መራቅ ማስተዋል ነው’ አለው።”
← Chapter 27
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 29 →
All chapters:
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42