bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
/
Job 33
Job 33
Amharic NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
← Chapter 32
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 34 →
1
“አሁን ግን ኢዮብ ሆይ፣ ንግግሬን ስማ፤ የምለውንም ሁሉ አድምጥ።
2
እንግዲህ አፌን እከፍታለሁ፤ አንደበቴም ይናገራል።
3
ቃሌ ከቅን ልብ ይወጣል፤ ከንፈሬም የማውቀውን በትክክል ይናገራል።
4
የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጥሮኛል፤ ሁሉን የሚችለውም አምላክ እስትንፋስ ሕይወት ሰጥቶኛል።
5
የምትችል ከሆነ መልስልኝ፤ ተዘጋጅተህም በፊቴ ቁም።
6
በእግዚአብሔር ፊት እኔም እንደ አንተው ነኝ፤ የተፈጠርሁትም ደግሞ ከዐፈር ነው።
7
እኔን መፍራት የለብህም፤ እጄም ሊከብድብህ አይገባም።
8
“በርግጥ የተናገርኸውን ሰምቻለሁ፤ እንዲህም ስትል አድምጫለሁ፤
9
‘ኀጢአት የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ፤ ከበደል ነጻ ነኝ፤ እድፈትም የለብኝም፤
10
እግዚአብሔር ግን ሰበብ ፈልጎብኛል፤ እንደ ጠላቱም ቈጥሮኛል፤
11
እግሬን በግንድ አጣብቋል፤ እንቅስቃሴዬንም ሁሉ ይከታተላል።’
12
“ነገር ግን እግዚአብሔር ከሰው ስለሚበልጥ፣ ትክክል እንዳልሆንህ እነግርሃለሁ።
13
የሰውን አቤቱታ እንደማይሰማ፣ ለምን ታማርርበታለህ?
14
ሰው ባያስተውለውም፣ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፤
15
ሰዎች ዐልጋቸው ላይ ተኝተው ሳሉ፣ ከባድ እንቅልፍ ሲወድቅባቸው፣ በሕልም፣ በሌሊትም ራእይ ይናገራል።
16
በጆሯቸው ይናገራል፤ በማስጠንቀቂያም ያስደነግጣቸዋል፤
17
ሰውን ከክፉ ሥራው ይመልሳል፤ ከትዕቢት ይጠብቃል፤
18
ነፍሱን ከጕድጓድ፤ ሕይወቱንም ከሰይፍ ጥፋት ያድናል።
19
ደግሞም ሰው ታምሞ በዐልጋው ላይ ሳለ፣ በዐጥንቱ የዘወትር ሥቃይ ይገሥጸዋል፤
20
ያኔም ሕይወቱ መብልን ትጠላለች፤ ነፍሱም ምርጥ ምግብን ትጠየፋለች።
21
እንዳልነበረ ሆኖ ሥጋው ይመነምናል፤ ተሸፍኖ የነበረው ዐጥንቱም ገጥጦ ይወጣል።
22
ነፍሱ ወደ ጕድጓድ፣ ሕይወቱም ወደ ሞት መልእክተኞች ትቀርባለች።
23
“ሆኖም ትክክለኛውን መንገድ ለሰው ያመለክት ዘንድ፣ መካከለኛም ይሆንለት ዘንድ፣ ከሺሕ አንድ መልአክ ቢገኝ፣
24
ለሰውየውም በመራራት፣ ‘ቤዛ አግኝቼለታለሁና፣ ወደ ጕድጓድ እንዳይወርድ አድነው’ ቢለው፣
25
በዚህ ጊዜ ሥጋው እንደ ሕፃን ልጅ ገላ ይታደሳል፤ ወደ ወጣትነቱም ዘመን ይመለሳል።
26
ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፤ ሞገስም ያገኛል፤ የእግዚአብሔርን ፊት ያያል፤ ሐሤትም ያደርጋል፤ እግዚአብሔር ወደ ጽድቅ ቦታው ይመልሰዋል።
27
ከዚያም ወደ ሰዎች መጥቶ እንዲህ ይላል፤ ‘ኀጢአትን ሠርቻለሁ፤ ትክክል የሆነውን አጣምሜአለሁ፤ ነገር ግን የእጄን አላገኘሁም።
28
ነፍሴ ወደ ጕድጓድ እንዳትወርድ፣ ታድጓታል፤ በሕይወትም ሆኜ ብርሃን አያለሁ።’
29
“እግዚአብሔር ይህን ሁሉ፣ ሁለት ሦስት ጊዜ ለሰው ያደርጋል።
30
ይኸውም የሕይወት ብርሃን ይበራለት ዘንድ፣ ነፍሱን ከጕድጓድ ለመመለስ ነው።
31
“ኢዮብ ሆይ፤ ልብ ብለህ ስማኝ፤ እኔ ልናገር፤ አንተ ዝም በል።
32
የምትለው ካለህ፣ መልስ ስጠኝ፤ ትክክለኛነትህንም ማወቅ እፈልጋለሁና ተናገር፤
33
አለዚያ፣ ዝም ብለህ ስማኝ፤ እኔም ጥበብን አስተምርሃለሁ።”
← Chapter 32
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 34 →
All chapters:
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42