bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
/
Job 28
Job 28
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
← Chapter 27
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 29 →
1
“በእውነቱ ማዕድን ተቈፍሮ ብር የሚወጣበትና ወርቅ የሚጣራበት ቦታ አለ።
2
ብረት ከመሬት ይገኛል፤ መዳብም ከማዕድን ድንጋይ ቀልጦ ይወጣል።
3
ሰዎች ጨለማን በማስወገድ እስከ መሬቱ ጥልቀት ዘልቀው በመግባት ራቅ ብሎ ወደሚገኘው ውስጥ በመግባት በድቅድቅ ጨለማው ውስጥ የማዕድን ድንጋይ ይፈልጋሉ።
4
ሰው ከሚኖርበት ቦታ ርቀው፥ የሰው እግር ረግጦት ወደማያውቅ ስፍራ ይደርሳሉ። እዚያም ጥልቅ ጒድጓድ ይቈፍራሉ፤ በገመድም ላይ እየተንጠለጠሉ፥ ከሰው ተለይተው ብቻቸውን ይሠራሉ።
5
ምድር ለምግብ የሚሆን እህል ታበቅላለች። ውስጥዋ በእሳት ቀልጦ ይገለባበጣል።
6
ሰንፔር የተባለው ዕንቊ በድንጋዮችዋ ውስጥ ይገኛል፤ በዐፈርዋም ውስጥ ወርቅ ይገኛል።
7
ወደ ማዕድኑ የሚወስደውን መንገድ ጭልፊት አያውቀውም፤ የአሞራም ዐይን አላየውም።
8
ክፉ አውሬዎች ያን ቦታ አልረገጡትም፤ አንበሳም በዚያ በኩል አላለፈም።
9
“ሰው መሬትን ሲቆፍር እጆቹን በሰላ ድንጋይ ላይ ያኖራል። ተራራዎችንም ከመሠረታቸው ይገለብጣል።
10
አለትን ሰንጥቆ መሿለኪያ መንገድ ያበጃል፤ ውድ የሆኑ የማዕድን ድንጋዮችንም ያገኛል።
11
የወንዞቹን ምንጮች ይገድባል፤ በምድር ውስጥ የተደበቀውንም ሀብት ያገኛል።
12
ታዲያ፥ ጥበብ ከየት ትገኛለች? ማስተዋልስ ቦታዋ የት ነው?
13
“ጥበብ ሕይወት ያላቸው ፍጥረቶች በሚኖሩባት ምድር አትገኝም፤ እውነተኛ ዋጋዋንም የሚያውቅ ሰው የለም።
14
‘ውቅያኖስ በእኔ ውስጥ የለችም’ ይላል፤ ‘ባሕሩም ከእኔ ጋር አይደለችም’ ይላል።
15
ጥበብ በንጹሕ ወርቅ አትገዛም፤ ዋጋዋም በብር አይተመንም።
16
ጥበብ ኦፊር ከሚባል ወርቅና፥ መረግድና ሰንፔር ከሚባሉ ዕንቆች የከበረች ናት።
17
ወርቅና የጠራ መስተዋት አይስተካከሉአትም፤ ከንጹሕ ወርቅ በተሠራ ጌጥም አትለወጥም።
18
የከበሩ ዛጐልና አልማዝ ከጥበብ ጋር አይወዳደሩም። የጥበብ ዋጋ ከሉልም በላይ ነው።
19
‘ቶጳዝዮን’ የተባለ የኢትዮጵያ ዕንቊ አይተካከላትም፤ እጅግ በጠራ ወርቅም አትገመትም።
20
ታዲያ፥ ጥበብ ከየት ትመጣለች? ማስተዋልስ ከወዴት ትገኛለች?
21
“ከሕያው ፍጡር ሁሉ የተሰወረች ናት፤ በሰማይ የሚበሩ ወፎች እንኳ ፈልገው አያገኙአትም።
22
ጥፋትና ሞት ‘ስለ እርስዋ የምናውቀው፥ በወሬ ብቻ ነው’ ይላሉ።
23
“ወደ ጥበብ የሚወስደውን መንገድና መኖሪያ ቦታዋንም የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
24
እርሱም የምድርን ዳርቻ ሁሉ ይመለከታል፤ ከሰማይ በታች ያለውን ሁሉ ያያል።
25
የነፋስን ኀይል በመሠረተ ጊዜ፥ የውቅያኖስን ውሃ በሰፈረ ጊዜ፥
26
ዝናብና ለነጐድጓዳዊ መብረቅ ሥርዓትን በደነገገ ጊዜ፥
27
እግዚአብሔር ጥበብን ተመለከታት ገምግሞም አከበራት፤ መርምሮም አጸናት።
28
“በዚያን ጊዜ ሰውን ‘እነሆ፥ ጥበብ ማለት እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ማስተዋልም ማለት ከክፋት መራቅ ነው’ ብሎታል።”
← Chapter 27
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 29 →
All chapters:
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42