bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
/
Job 34
Job 34
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
← Chapter 33
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 35 →
1
ኤሊሁም ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ አለ፦
2
“እናንተ ጠቢባን የምናገረውን ስሙኝ፤ እናንተም ዐዋቂዎች አድምጡኝ።
3
የምግብ ጣዕም በምላስ እንደሚታወቅ፥ ንግግርም በጆሮ ይለያል።
4
ትክክለኛ የሆነውን ነገር መርምረን እንወቅ፤ መልካሙንም ነገር አብረን እንማር።
5
ኢዮብ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤ እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነፈገኝ።
6
እኔ እውነተኛ ስሆን፥ እንደ ውሸተኛ ተቈጠርኩ፤ ምንም በደል ሳይኖርብኝ በማይፈወስ ቊስል እሠቃያለሁ’ ብሎአል።
7
“እንደ ኢዮብ በእግዚአብሔር ላይ የሚያፌዝ ሰው ከቶ ይገኛልን?
8
ጓደኞቹ ክፉ አድራጊዎች ናቸው፤ የሚውለውም ከክፉ አድራጊዎች ጋር ነው።
9
‘እግዚአብሔርን ማስደሰት፥ ለሰው ምንም አይጠቅመውም’ ይላል።
10
“አስተዋዮች የሆናችሁ ሰዎች አድምጡኝ! ክፋትን ማድረግ ከእግዚአብሔር፥ ስሕተትንም ማድረግ ሁሉን ከሚችል አምላክ ይራቅ!
11
እግዚአብሔር ለሰው እንደ ሥራው ይከፍለዋል፤ በአካሄዱም መጠን የሚገባውን ያደርግለታል።
12
ሁሉን የሚችል አምላክ ከቶ ክፉ ነገር አያደርግም፤ በማንኛውም ሰው ላይ ፍርድን አያዛባም።
13
ምድርን ለእግዚአብሔር ዐደራ የሰጠው የለም፤ በዓለም ላይ ኀላፊ አድርጎ የሾመው የለም።
14
እግዚአብሔር መንፈሱንና እስትንፋሱን ወደ ራሱ ለመመለስ ቢያስብ፥
15
የሰው ዘር ሁሉ በአንድነት በጠፋ ነበር፤ ወደ ዐፈርም በተመለሰ ነበር።
16
አስተዋይ ብትሆን ይህን ስማ፤ ንግግሬንም አድምጥ።
17
ፍትሕን የሚጠላ መግዛት ይችላልን? ጻድቁንና ኀያሉን እግዚአብሔር በደለኛ ታደርገዋለህን?
18
ንጉሡን የማትጠቅም ነህ፤ መኳንንቱንም ክፉዎች ናችሁ፤ የሚላቸው ማነው?
19
ሁሉም የእጁ ሥራዎች ስለ ሆኑ፤ እርሱ ለመኳንንቱ አያደላም ባለጸጋውን ከድኻው አይለይም።
20
ሰዎች በእኩለ ሌሊት በቅጽበት ሊሞቱ ይችላሉ። ተንቀጥቅጠውም ያልፋሉ። ኀያላንም የማንም ሰው እጅ ሳይነካቸው ይወገዳሉ።
21
እግዚአብሔር የሰዎችን ሁሉ እርምጃ ይመለከታል። የእያንዳንዳቸውን እርምጃ ይቈጣጠራል።
22
ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፤ ድቅድቅ ጨለማ ከቶ የለም።
23
በእግዚአብሔር ፊት ለፍርድ ለመቅረብ ቀጠሮ አይሰጣቸውም።
24
ገዢዎችን ከሥልጣናቸው አውርዶ፥ በቦታቸው ሌሎችን ለመተካት፥ ምርመራ አያስፈልገውም።
25
ስለዚህም ሥራቸውን ዐውቆ፥ በአንድ ሌሊት ከሥልጣናቸው አስወግዶ ያጠፋቸዋል።
26
በሠሩት ዐመፃ ምክንያት ኃጢአተኞችን በሰው ፊት ይቀጣቸዋል።
27
ይህንንም የሚያደርግባቸው፥ እርሱን መከተል ስለ ተዉና ትእዛዞቹንም ስለ ናቁ ነው።
28
ድኾችን በመጨቈን ወደ እግዚአብሔር እንዲጮኹ አድርገዋቸዋል፤ እግዚአብሔርም የድኾችን ጩኸት ሰምቶአል።
29
“እግዚአብሔርን የሚክድና ሕዝቡን የሚያጠምድ ንጉሥ ሲነግሥ፥ እግዚአብሔር ዝም ቢል፥ ወይም ፊቱን ቢሰውር ማን ሊወቅሰው ይችላል?
31
“ምናልባት አንድ ሰው ለእግዚአብሔር ‘እስከ አሁን በድዬአለሁ ዳግመኛ አልበድልም፥
32
የሠራሁት ኃጢአት የትኛው እንደ ሆነ አስተምረኝ፤ በድዬም ከሆነ፥ ዳግመኛ አልሠራም’ ያለው ሰው አለን?
33
ታዲያ፥ አንተ ንስሓ መግባት እንቢ እያልክ፥ አንተ በምታቀርበው ሐሳብ መሠረት እግዚአብሔር ምኞትህን እንዲፈጽምልህ ትፈልጋለህን?
34
“የሚሰሙኝ ሰዎች እንዲህ ይሉኛል፤ የሚያስተውሉ ሰዎች እንዲህ ይላሉ፦
35
‘ኢዮብ የሚናገረው ያለ ዕውቀት ነው፤ ንግግሩም ፍሬ ቢስ ነው’
36
የክፉዎች ሰዎችን የመሰለ መልስ ስለሚሰጥ ምነው ኢዮብ እስከ መጨረሻው ድረስ በተፈተነ!
37
በመካከላችን ሕገ ወጥ በመሆን፥ በእግዚአብሔር ላይ ንቀትን በማብዛት ኢዮብ በኃጢአቱ ላይ ዐመፅን ጨምሮአል።”
← Chapter 33
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 35 →
All chapters:
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42