bible
ra
🌐 Language
English
Español
Français
Deutsch
Português
Italiano
Nederlands
Русский
中文
日本語
한국어
العربية
Türkçe
Tiếng Việt
ไทย
Indonesia
All Languages
Home
/
Amharic
/
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
/
Job 33
Job 33
Amharic New Standard Translation (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም) 2005
← Chapter 32
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 34 →
1
“አሁንም ኢዮብ ሆይ! የምነግርህን ስማኝ፤ የምልህንም ሁሉ በጥንቃቄ አድምጠኝ፤
2
መልስ ልሰጥህ ተዘጋጅቻለሁ፥ አንደበቴም ለመናገር ተዘጋጅቶአል።
3
ቃሎቼ የልቤን ቅንነት ይገልጣሉ፤ ምላሶቼም እውነቱን ይናገራሉ።
4
የፈጠረኝ የእግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ ሕይወትም የሰጠኝ ሁሉን የሚችል አምላክ እስትንፋስ ነው።
5
“የምትችል ከሆነ ለንግግሬ መልስ ስጠኝ፤ ክርክሮችህን አመቻችተህ ቆመህ ተከራከረኝ።
6
እነሆ፥ እኔና አንተ በእግዚአብሔር ፊት እኩል ነን፤ እኔም የተፈጠርኩት ከጭቃ ነው።
7
እኔን መፍራት አይገባህም፤ እኔ ተጽዕኖ ላሳድርብህ አልችልም።
8
“በእርግጥ እኔ የተናገርከውን ሁሉ ሳዳምጥ ቈይቼአለሁ፤ ከአንደበትህም የወጡትን ቃላት ሰምቼአለሁ።
9
አንተ ስትናገር ‘በደልና እንከን የሌለብኝ፥ ከኃጢአት ንጹሕ የሆንኩ፥ ነጻ ነኝ፤
10
ነገር ግን እግዚአብሔር እኔን ለመቅጣት ምክንያት ይፈልግብኛል እንደ ጠላትም ይቈጥረኛል፥
11
እግሮቼን በግንድና በግንድ መካከል አጣብቆ ይይዛል፤ በምሄድበት መንገድ ሁሉ ይመለከተኛል።’ ብለሃል።
12
“ኢዮብ ሆይ! ይህ ንግግርህ ስሕተት መሆኑን ልገልጥልህ እወዳለሁ፤ እግዚአብሔር ከሰው ሁሉ ይበልጣል።
13
ታዲያ፥ ‘እግዚአብሔር የሰውን አቤቱታ አይሰማም’ በማለት ለምን በእግዚአብሔር ላይ ታማርራለህ?
14
ሰው አያስተውልም እንጂ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል።
15
በሌሊት ሰዎች በአልጋ ላይ ተኝተው አፍላ እንቅልፍ ይዞአቸው ሳለ፥ እግዚአብሔር በሕልምና በራእይ ይናገራል።
16
በዚያም ጊዜ ሰዎች ቃሉን እንዲሰሙ ያደርጋል፤ በሚሰጣቸውም ማስጠንቀቂያ ያስደነግጣቸዋል።
17
በዚህ ዐይነት ሰዎች ኃጢአት ከመሥራት እንዲቈጠቡ ያደርጋል፤ ትዕቢትንም ከእነርሱ ያስወግዳል።
18
ሕይወታቸውንም ከጥፋት ይጠብቃል፤ ከሞት መቅሠፍትም ይታደጋቸዋል።
19
ወይም እንደገና ሰው በአጥንቱ ውስጥ በማያቋርጥ በሽታ በአልጋ ቊራኛነት እንዲገሠጽ ያደርጋል።
20
በዚህ ዐይነት ሕመምተኛው እህል መቅመስን ያስጠላዋል፤ ምርጥ የሆነ ምግብ እንኳ አያስደስተውም።
21
ከመክሳቱ የተነሣ ሥጋው አልቆ አጥንቱ ወጥቶ ይታያል።
22
ሕይወቱ አልፎ ነፍሱ ወደ ሙታን ዓለም ለመውረድ ተቃርባለች።
23
“ለሰው ትክክለኛውን መንገድ ከሚያመለክቱት፥ በሺህ ከሚቈጠሩ የእግዚአብሔር መላእክት አንዱ ወደ እርሱ መጥቶ ይረዳው ይሆናል፤
24
መልአኩም አዝኖለት ‘ቤዛ ያገኘሁለት ስለ ሆነ፥ ወደ መቃብር እንዳይወርድ፥ ተወው!’ ብሎ ሞትን ያዘዋል።
25
ስለዚህ ሥጋው እንደገና እንደ ልጅ ሥጋ ሆኖ ይታደሳል፤ እንደ ወጣትነቱም ጊዜ ይመለሳል።
26
በዚያን ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፤ ጸሎቱንም እግዚአብሔር ይሰማዋል የእግዚአብሔርን ፊት አይቶ ይደሰታል፤ እግዚአብሔርም ስለጽድቁ ዋጋውን ይከፍለዋል።
27
እርሱም በሰዎች ፊት እንዲህ ብሎ ይዘምራል፤ ‘እኔ ኃጢአት ሠርቻለሁ፤ የቀናውንም ነገር አጣምሜአለሁ፤ እግዚአብሔር ግን በደሌን አልቈጠረብኝም።
28
ወደ ሙታን ዓለም ከመውረድም አዳነኝ፤ እነሆ፥ አሁን በሕይወት ተገኝቼ ብርሃንን አያለሁ።’
29
“እነሆ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ነገር ለሰዎች መላልሶ ያደርጋል።
30
የሕይወትን ብርሃን እንዲያይ፥ ነፍሱን ከመቃብር ይመልሰዋል።
31
“ኢዮብ ሆይ! የምነግርህን በጥንቃቄ አድምጥ፤ እስቲ አንተ ዝም በልና እኔ ልናገር።
32
የምትለው ነገር ካለህ መልስልኝ፤ እኔ አንተን ነጻ ለማውጣት ስለምፈልግ ተናገር።
33
አለበለዚያ ዝም ብለህ እኔ የምናገረውን ስማ፤ እኔም ጥበብን አስተምርሃለሁ።”
← Chapter 32
Jump to:
Chapter 1
Chapter 2
Chapter 3
Chapter 4
Chapter 5
Chapter 6
Chapter 7
Chapter 8
Chapter 9
Chapter 10
Chapter 11
Chapter 12
Chapter 13
Chapter 14
Chapter 15
Chapter 16
Chapter 17
Chapter 18
Chapter 19
Chapter 20
Chapter 21
Chapter 22
Chapter 23
Chapter 24
Chapter 25
Chapter 26
Chapter 27
Chapter 28
Chapter 29
Chapter 30
Chapter 31
Chapter 32
Chapter 33
Chapter 34
Chapter 35
Chapter 36
Chapter 37
Chapter 38
Chapter 39
Chapter 40
Chapter 41
Chapter 42
Chapter 34 →
All chapters:
1
2
3
4
5
6
7
8
9
10
11
12
13
14
15
16
17
18
19
20
21
22
23
24
25
26
27
28
29
30
31
32
33
34
35
36
37
38
39
40
41
42